04/18/2020
በጎነት ቀጥሏል!!
"ራይድ" ለኢትዮጵያ ሃኪሞች ማህበር 50,000 የአፍ መሸፈኛ ማስኮችን አበርክቷል ።
ራይድ የኮቪድ 19 ወረርሺኝ ስጋት በሃገራችን ከተከሰተ ጀምሮ ለተለያዩ የማህረሰብ ክፍሎች ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ከድርጅቱ ጋር አብረው ለሚሰሩ 15,000 (አስራ አምስት ሺ) ያህል አሽከርካሪዎች፤ ለሶስት ሺ የላዳ አሽከርካሪዎች በተጨማሪም በአስሩም ክፍለ ከተሞች ለሚገኙ የትራፊክ ፖሊሶችን ጨምሮ የአፍ መሸፈኛ ማስኮችን እና የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር ማበርከቱ ይታወቃል።
ዛሬ ለሃኪሞች ማህበር የተደረገው የቁሳቁስ ድጋፍ አንድ ሚሊየን አራት መቶ ሺ ብር መሆኑን የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሪት ሳምራዊት ፍቅሩ ነግረውናል።